በጀርመን አገር በሙኒክ ከተማ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያንና ትውልደኢትዮጵያዊያን በሀገራቸውየኮሮናቫይረስ ወረርሺኝን ለመከላከል እንዲቻል 8558,00€ የገንዝብ እርዳታ አደረጉ

በጀርመን አገር በሙኒክ ከተማ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያንና ትውልደ ኢትዮጵያዊያን እንደ ሌሎች በውጭ አገር የሚኖሩ ወገኖቻቸው በኢትዮጵያ የኮረና ቫይረስ ወረርሺኝን ለመከላከል በሚደረገው ርብርብ ላይ የበኩላቸውን አስተዋፅኦ እንዲያደርጉ ከፍራንክፈርት የኢፌዲሪ ኮንሱላት ጽ/ቤት የቀረበውን የዜግነት ጥሪ መነሻ በማድረግ በየኢትዮጵያውያን ኮሚዩኒቲ በሙኒክ አስተባባሪነት ባለፉት ሳምንታት በኦን ላይን (Online) የተጀመረው የገንዘብ እርዳታ ማሰባሰብ የደረሰበትን ደረጃ በሚመለከት  የእያንዳንዱ ልገሳ ያደረጉ ወገኖችን ስምና የለገሱትን የገንዘብ መጠን የታዳጊ ወጣቶችን አስተዋፅኦ ጭምር በዝርዝር ለህብረተሰቡ ግልጽነት ባለው መንገድ በሰንጠርዥ በማቅረብ አሳውቀዋል ።

» Weiterlesen

ከመፃህፍት አለም ታላቁ ጥቁር ከተሰኘ መፅሐፍ የተወሰደ

ከዚህ ቀጥሎ በተለያዩ ክፍሎች የሚቀርቡት ጽሁፎች ከዚህ በላይ በምስል ከተቀመጠው ከለመድናቸውና ካነበብናቸው ለየት ያሉ ያልተሰሙ የአድዋ ድልና የአጤ ምኒሊክ ታሪኮችን ይዞ ለህዝብ ከቀረበው የአቶ ንጉሴ አየለ ተካ ‚ታላቁ ጥቁር ‚ የተሰኘ መፅሐፍ የተወሰዱ መሆናቸውን አስቀድመን ለመግለፅ እንወዳለን ። ልክ በዛሬው ቀን ፌብሩዋሪ 1,1094 እኤአ የምዕራቡ ዓለም ሪፓርተሮች ምን ዘገቡ? ሮበርት ስኪነርና አብረውት የነበሩት ባልደረቦቹ ከኢትዮጵያ ድሬዳዋ ፣ በጂቡቲ ከዚያም በቪክቶሪያ በተሰኘች መረከብ  አድርገው. ስኪነር ከ5አመታት በላይ ወደ ሰራባት ማርሴይ (ፈረንሳይ) ሲደርስ በፓሪስ የአሜሪካን ኤምባሲ ተወካይና  ብዙ ሌሎች ሠዎች „እንኳን ደህና መጣህ“ ለማለት ተሰብስበዋል ።ከስድስት ወራት በላይ የተለያት ባለቤቱ ሄለንም ነበረች።ነገር ግን ስለኢትዮጵያና ስለ ጥቁሩ የአቢሲኒያ ንጉስ ለመስማትና ሪፖርት ለማድረግ የተሰበሰቡት  የአውሮፓና የአሜሪካን የዜና ሪፓርተሮች ቦታውን አጨናንቀውት ነበር። ስኪነር በሪፓርተሮች ተከበበ!

» Weiterlesen

124ኛው የአድዋ ድል በዓል በሙኒክ ጀርመን በድምቀት ተከብሮ ውሏል።

ፌብሪዋሪ 22 ቀን 2020 እ/ኤ/አ በጀርመን ከተማ በሙኒክ ከተማ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያንና ትውልደ ኢትዮጵያውያን በአንድ ላይ ተሰባስበው 124ኛውን የአድዋ ድል በአል በሙኒክ የኢትዮጵያውያን ኮሚኒዩቲ አስተባባሪነት በደመቀ ሁኔታ አክብረዋል። በበአሉ ላይ በሙኒክና አካባቢው የሚኖሩ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያንና ትውልደ ኢትዮጵያውያን ከቤተሰቦቻቸው ጋር የተገኙ ሲሆን በተጨማሪ በጀርመን የኢፌዲሪ ኤምባሲን በመወከል በፍራንክፈርት የኢፌዲሪ ቆንስላ አምባሳደር በረደድ አንሙት በእንግድነት ተገኝተዋል።  በአሉን በንግግር የከፈቱት በሙኒክ የኢትዮጵያውያን ኮሚዩኒቲ ሊ/መንበር ወ/ሮ ዘነብ ወርቅ አድነው ሲሆኑ በንግግራቸው የአድዋ ድል በዓል የኢትዮጵያውያን ድል ብቻ ሳይሆን የመላው ጥቁር ህዝቦች በአል ሆኖ አፍሪካውያን ሁሉ የሚኮሩበት ድል ሆኖ ሳለ በእኛው በኢትዮጵያውያን የተሰጠው ትኩረት የሚገባውን ያህል አለመሆኑ በተጻራሪው ታሪክን ለማኮሰስና በሎም ለማጥፋት ለሚሰሩ የውስጥም ሆነ የውጪ ጠላቶች አመቺ ሁኔታን ፈጥሯል በማለት ገልጸዋል። ከዚህም በተጭማሪ ተተኪው ትውልድ ታሪክን በአግባቡ እንዳይረዳና እንዳይረከብ ሆኗል። ስለዚህም አሁንም አለመርፈዱንና እኛ ወላጆች ጠንክረን ከሰራን ታሪካቸውን ለመረከብ የተዘጋጁ ለጆቻችን አሉና እኛ ከኛ የሚጠበቅብንን እንስራ ሲሉ ጥሪያቸውን አቅረበዋል።

» Weiterlesen