የአቶ ብሩክ ማሞ አጭር የሕይወት ታሪክ

2 Timothy 4:7-8 / 2ኛ ጢሞ 4 ፣ 7-8Ich habe den guten Kampf gekämpft, den Lauf vollendet, den Glauben bewahrt; hinfort liegt für mich die Krone der Gerechtigkeit bereit; መልካሙን ገድል ተጋድዬአለሁ፥ ሩጫውን ጨርሼአለሁ፥ ሃይማኖትን ጠብቄአለሁ፤ ወደ ፊት የጽድቅ አክሊል ተዘጋጅቶልኛል፥ I have fought the good fight, I have finished the race, I have kept the faith. Henceforth there is laid up for me the crown of righteousness, which the Lord, the righteous judge, will award to me on that day በወ/ሮ እናኑ ጌታሁን የቀረበ ወንድማችን አቶ ብሩክ ማሞ ወይም በክርስትና ስሙ ተክለ አረጋዊ ሰኔ 6 ቀን 1955 ዓ.ም በአዲስ አበባ ከተማ ተወለደ። በአዲስ አበባ ቢወለድም የወጣትነት እድሜዉንና ትምህርቱን የተከታትለው በቀደሞ ስሙ በጅባትና ሜጫ አውራጃ በአምቦ ክተማ ነዉ። እንደማንኛውም ህጻን በዚያን ዘመን በቄስ ት/ቤ ፊደል ቆጥሮ የአንደኛ ደረጃ ትምህርቱን በአምቦ ት/ቤት በጥሩ ሁኔታ ስላጠናቀቀ፣ የ2ተኛ ደረጃ ትምህርቱን በአዲሰ አበባ ጄኔራል ዊንጌት አዳሪ ት/ቤት ለመማር እድል አገኝቶ ለ4 ዓመታት ትምህርቱን ተከታትሏል። በጥሩ ውጤትም አጠናቋል።  

» Weiterlesen