ከሰው ማሣ አትጨድ!

ተዋናይ ፣ አዘጋጅ ፣ ገጣሚ እና አርቲስት ፣ የጣይቱ የባህል ማዕከል በዋሺንግተን ዲሲ መስራች አለም ፀሃይ ወዳጆ ከሰው ማሣ አትጨድ! ከሰው ማሳ አትጨድ …የንጥቂያ ከፍታ መሬት ታውላለች፤እያንዳንዷ ውጤት …እያንዳንዷ ፍሬ ዋጋ አስከፍላለች፡ጥረህ ግረህ ብላ …እንደ መፅሐፉ ቃል፡ዛሬም ባይሆን ነገ የሰው ወዙ ያንቃል፤አፈሩን ጎልጉሎ … ቆፍሮ አረስርሶ፡ዘርቶ ተንከባክቦ ….ከእንቅልፉ ቀንሶ፤ለዝናብ አንጋጦ ….ፀሐይን ተማልዶ፡መዳፉን አሻክሮ …ልምዱን አዋሕዶ፤በውኑም በእንቅልፉም ፡ሲያስብ ከርሞበታል፡ፍሬው እስኪያፈራ ፡ ሥቃይ ቆጥሮበታል፤ከሰው ማሳ አትጨድ ! …በጨለማ ተገን ፤ እንዳይቀጨው አውሬ፡እንዳያዳባየው ፡ ረግጦ ተራምዶበትግድ አይሰጠው ጥሬ …አጥሮ ጠብቆት ነው ውጤት ሆኖ አብቦ ይህ ያየኸው ዛሬ፤እያንዳንዷ ውጤት …እያንዳንዷ ፍሬ ዋጋ አስከፍላለች፡ከሰው ማሳ አትጨድ …የንጥቂያ ከፍታ መሬት ታውላለች፤ጥረህ ግረህ ብላ …እንደ መፅሃፉ ቃል፡ዛሬም ባይሆን ነገ …. የሰው ወዙ ያንቃል፤በግንባር ፡ በላብህ በጉልበትህ ጥረት ፡በራስህ ተመንደግ በድካምህ ውጤትከሰው ማሣ አትጨድ…ዝም ብሎ አላፈራም እንዲያው እንደዘበት … ዘለህ አትፈሰው…ንቀህ ወይ ዘንግተህ የደከመበትን የፈጠረውን … ሰው ፤በየቱም ሙያ መስክ …በምንም ሥራ ላይደክመህ መመንደግ ነው … ከልብ የሚያረካው .. ስትውል ከበላይጤና ተገብሮ ተስፋ ተሰንቆ ፡በቁር በሐሩሩ …. ተጥሎ ተወድቆ፤የጋሬጣ ፍቀት … ያደማ እሾህ ታልፎ ፡የለማ ፍሬ ነው …ከዕድሜ ላይ ተቀርፎ ፤ከሰው ማሣ አትጨድ !

» Weiterlesen

ከመፃህፍት አለም ታላቁ ጥቁር ከተሰኘ መፅሐፍ የተወሰደ

ከዚህ ቀጥሎ በተለያዩ ክፍሎች የሚቀርቡት ጽሁፎች ከዚህ በላይ በምስል ከተቀመጠው ከለመድናቸውና ካነበብናቸው ለየት ያሉ ያልተሰሙ የአድዋ ድልና የአጤ ምኒሊክ ታሪኮችን ይዞ ለህዝብ ከቀረበው የአቶ ንጉሴ አየለ ተካ ‚ታላቁ ጥቁር ‚ የተሰኘ መፅሐፍ የተወሰዱ መሆናቸውን አስቀድመን ለመግለፅ እንወዳለን ። ልክ በዛሬው ቀን ፌብሩዋሪ 1,1094 እኤአ የምዕራቡ ዓለም ሪፓርተሮች ምን ዘገቡ? ሮበርት ስኪነርና አብረውት የነበሩት ባልደረቦቹ ከኢትዮጵያ ድሬዳዋ ፣ በጂቡቲ ከዚያም በቪክቶሪያ በተሰኘች መረከብ  አድርገው. ስኪነር ከ5አመታት በላይ ወደ ሰራባት ማርሴይ (ፈረንሳይ) ሲደርስ በፓሪስ የአሜሪካን ኤምባሲ ተወካይና  ብዙ ሌሎች ሠዎች „እንኳን ደህና መጣህ“ ለማለት ተሰብስበዋል ።ከስድስት ወራት በላይ የተለያት ባለቤቱ ሄለንም ነበረች።ነገር ግን ስለኢትዮጵያና ስለ ጥቁሩ የአቢሲኒያ ንጉስ ለመስማትና ሪፖርት ለማድረግ የተሰበሰቡት  የአውሮፓና የአሜሪካን የዜና ሪፓርተሮች ቦታውን አጨናንቀውት ነበር። ስኪነር በሪፓርተሮች ተከበበ!

» Weiterlesen