ከመፃህፍት አለም ታላቁ ጥቁር ከተሰኘ መፅሐፍ የተወሰደ

ከዚህ ቀጥሎ በተለያዩ ክፍሎች የሚቀርቡት ጽሁፎች ከዚህ በላይ በምስል ከተቀመጠው ከለመድናቸውና ካነበብናቸው ለየት ያሉ ያልተሰሙ የአድዋ ድልና የአጤ ምኒሊክ ታሪኮችን ይዞ ለህዝብ ከቀረበው የአቶ ንጉሴ አየለ ተካ ‚ታላቁ ጥቁር ‚ የተሰኘ መፅሐፍ የተወሰዱ መሆናቸውን አስቀድመን ለመግለፅ እንወዳለን ። ልክ በዛሬው ቀን ፌብሩዋሪ 1,1094 እኤአ የምዕራቡ ዓለም ሪፓርተሮች ምን ዘገቡ? ሮበርት ስኪነርና አብረውት የነበሩት ባልደረቦቹ ከኢትዮጵያ ድሬዳዋ ፣ በጂቡቲ ከዚያም በቪክቶሪያ በተሰኘች መረከብ  አድርገው. ስኪነር ከ5አመታት በላይ ወደ ሰራባት ማርሴይ (ፈረንሳይ) ሲደርስ በፓሪስ የአሜሪካን ኤምባሲ ተወካይና  ብዙ ሌሎች ሠዎች „እንኳን ደህና መጣህ“ ለማለት ተሰብስበዋል ።ከስድስት ወራት በላይ የተለያት ባለቤቱ ሄለንም ነበረች።ነገር ግን ስለኢትዮጵያና ስለ ጥቁሩ የአቢሲኒያ ንጉስ ለመስማትና ሪፖርት ለማድረግ የተሰበሰቡት  የአውሮፓና የአሜሪካን የዜና ሪፓርተሮች ቦታውን አጨናንቀውት ነበር። ስኪነር በሪፓርተሮች ተከበበ!

» Weiterlesen