124ኛው የአድዋ ድል በዓል በሙኒክ ጀርመን በድምቀት ተከብሮ ውሏል።

ፌብሪዋሪ 22 ቀን 2020 እ/ኤ/አ በጀርመን ከተማ በሙኒክ ከተማ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያንና ትውልደ ኢትዮጵያውያን በአንድ ላይ ተሰባስበው 124ኛውን የአድዋ ድል በአል በሙኒክ የኢትዮጵያውያን ኮሚኒዩቲ አስተባባሪነት በደመቀ ሁኔታ አክብረዋል። በበአሉ ላይ በሙኒክና አካባቢው የሚኖሩ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያንና ትውልደ ኢትዮጵያውያን ከቤተሰቦቻቸው ጋር የተገኙ ሲሆን በተጨማሪ በጀርመን የኢፌዲሪ ኤምባሲን በመወከል በፍራንክፈርት የኢፌዲሪ ቆንስላ አምባሳደር በረደድ አንሙት በእንግድነት ተገኝተዋል።  በአሉን በንግግር የከፈቱት በሙኒክ የኢትዮጵያውያን ኮሚዩኒቲ ሊ/መንበር ወ/ሮ ዘነብ ወርቅ አድነው ሲሆኑ በንግግራቸው የአድዋ ድል በዓል የኢትዮጵያውያን ድል ብቻ ሳይሆን የመላው ጥቁር ህዝቦች በአል ሆኖ አፍሪካውያን ሁሉ የሚኮሩበት ድል ሆኖ ሳለ በእኛው በኢትዮጵያውያን የተሰጠው ትኩረት የሚገባውን ያህል አለመሆኑ በተጻራሪው ታሪክን ለማኮሰስና በሎም ለማጥፋት ለሚሰሩ የውስጥም ሆነ የውጪ ጠላቶች አመቺ ሁኔታን ፈጥሯል በማለት ገልጸዋል። ከዚህም በተጭማሪ ተተኪው ትውልድ ታሪክን በአግባቡ እንዳይረዳና እንዳይረከብ ሆኗል። ስለዚህም አሁንም አለመርፈዱንና እኛ ወላጆች ጠንክረን ከሰራን ታሪካቸውን ለመረከብ የተዘጋጁ ለጆቻችን አሉና እኛ ከኛ የሚጠበቅብንን እንስራ ሲሉ ጥሪያቸውን አቅረበዋል።

» Weiterlesen

የኢትዮጵያ አዲስ አመት 2012 ዓ/ም በሙኒክ ከተማ በድምቀት ተከብሯል

ethiopian new year 2012

በጀርመን አገር በሙኒክ ከተማ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያንና ትውልደ ኢትዮጵያውያን በጥቅምት 1 ቀን 2012 ዓ/ም ( እኤአ በኦክቶበር 12.2019) በኮሚኒዩቲያቸው አስተባባሪነት በኢትዮጵያውያን የዘመን አቆጣጠር አዲሱን ዓመት 2012ዓ/ምን  ባንድ ላይ ተስባስበው ቤተስባዊ መልክ ባለውና በደመቀ ሁኔታ አክብረዋል።

» Weiterlesen
1 2