በጀርመን አገር በሙኒክ ከተማ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያንና ትውልደ ኢትዮጵያውያን ፈጣን ምላሽ ለወገኔ በሚል ዝግጅት ከ15,000.00 € (አስራ አምስት ሺህ ዩሮ)በላይ አሰባሰቡ።

በሰሜኑ የሀገራችን ክፍል በአሸባሪው የህውሃት ቡድን እኔ ወደ የመንግስት ስልጣን ካልተመለስኩ ሀገር ትፍረስ በሚል ዕብሪት በቀሰቀሰው ጦርነት ሳቢያ ሰላማዊው የሀገራች ህዝብ በአሰቃቂ ሁኔታ ለመገደል ፣ንብረቱን ለመዘረፍ፣ለመቁሰልና ለመሰደድ መዳረጉን የሰሙ በሀገር ውስጥና ከገር ውጪ የሚኖሩ ሀገር ወዳድ ኢትዮጵያውያንና ትውልደ ኢትዮጵያውያን በከፍተኛ ቁጭትና ሀዘን ውስጥ ወድቀዋል።እነዚህ ይህ ቁጭትና ሀዘን እንቅልፍ የነሳቸው በመላው ዓለም የተለያዩ አገሮች የሚኖሩ ሀገር ወዳድ ኢትዮጵያውያንና ትውልደ ኢትዮጵያውያን በግልና በተለያዩ  መልክ ተደራጅተው የገንዘብ፣ የምግብና የአልባሳት ዕርዳታ ማሰባሰብና ለተጎጂዎች በማድረስ ላይ ሲረባረቡ ይስተዋላል። የኢትዮጵያውያን ኮሚዩኒቲ በሙኒክና አካባቢው ስር የተደራጁ ኢትዮጵያውያንና ትውልደ ኢትዮጵያውያንም እንደ ሌሎች ሀገር ወዳድ ወገኖቻቸው በወቅቱ የሀገራችን ጉዳይ ላይ መክረው በተደራጀ  የኢትዮጵያውያን ኮሚዩኒቲያቸው አስተባባሪነት የበኩላቸውን ለማድረግ በመነሳሳት ሁለት የዕርዳታ ማሰባቢያ ዕቅዶችን በማስቀመጥ ተንቀሳቅሰዋል። 1ኛው..ሀገርን የማዳን አስቸኳይ ጥሪ  በሚል መርህ ላይ የተመሰረተ ሲሆን።በየወሩ ለአንድ ዓመት የሚዘልቅ ለሀገርና ለወገን ለመድረስ የሚያስችል  የገንዘብ እርዳታ የማሰባሰብ እንቅስቃሴ ሲሆን2ኛው.ፈጣን ምላሽ ለተራበው፣ለተጠማውና ለታረዘው ወገኔ !* በሚል መርህ  ላይ የተመሰረተና ሀገር ወዳዶች የሚያደርጉትን በአንድ ጊዜና በአፋጣኝ የሚለግሱትን የገንዘብ ዕርዳታ ማሰባሰብ ነው።በእነዚህ  በሁለቱም ዕቅዶች መሰረት የተደረገው እንቅስቃሴ እጅግ አመርቂ የሆነ ውጤት መገኘቱን ከዝግጅቱ አስተባባሪ ኮሚቴዎች ሲገልጹ*ፈጣን ምላሽ ለተራበው፣ለተጠማውና ለታረዘው ወገኔ*በሚለው መርህ የኢትዮጵያ ኮሚዩኒቲ በሙኒክ በአካባቢው ለሚኖሩ ኢትዮጵያውያን የወገን ለወገን ይድረስ ጥሪውንበኦክቶበር 31.2021 ባዘጋጀው ልዩ ዝግጅት ከ15,000.00€ (አስራ አምስት ሺህ ዩሮ) በላይ ለማሰባሰብ መቻሉንና በሌላ በኩል በ1ኛ ደረጃ በተቀመጠው ዕቅድ መሰረት ሀገራችን የምትገኝበትንን እጅግ አስቸጋሪ ሁኔታ ግምት ውስጥ በማስገባት ኮሚዪኒቲው ሀገር ወዳድ ወገኖችን በማስተባበር በየወሩ እንደ መነሻ  50€ (ሃምሳ ዩሮ) አየተዋጣ  ለአንድ አመት የሚዘልቅ የገንዘብ ማሰባሰብ ስራ ከጀመረ እነሆ ሶስተኛ ወሩን መያዙንና የሚያበረታታ ውጤት እየታየበት መሆኑን ለመረዳት ተችሏል።በዚህ ለአንድ አመት የገንዘብ መዋጮ ላይ መሳተፍ ለሚፈልጉ ኢትዮጵያውያን ሁሉ ከዚህ መልዕክት ጋር በተቀመጠው ለዚሁ ሲባል በተዘጋጀው የባንክ አካውንት በየወሩ የተቻላቸውን ያህል Dauerauftrag ፣ ወይም የአመት፣ ሩብ አመት፣የስድስት ወር በማስተላለፍ  መሳተፍ የሚችሉ መሆኑም በተጨማሪ ተገልጿል።  ይህ በሙኒክና አካባቢው ኢትዮጵያውያን ኮሚዩኒቲ ከጥቂት ወራት በፊት *ደግሞ ለአባይ* በሚል ልዪ የግሪል ዝግጅት አዘጋጅቶ የቦንድ ሽያጭና የገንዘብ ልገሳ፣እንዲሁም የምግብና የመጠጥ ሺያጭ በጥቅሉ ከ20,000.00€(ሃያ ሺህ ዩሮ)  በላይ አሰባስቦ ለሚመለከተው ክፍል ማስተላለፉም ተገልጿል። ከሀገራችንና ከህዝባችን ጎን ለመቆምና እንደ ዜጋ የበኩላችንን ለመወጣት ከህሊናችን በስተቀር የማንንም ፈቃድ ወይም ይሁንታ አያስፈልገንም!!የህዝባችንን ህይወት ለመታደግ የምናቀርበው ምንም ምክንያት የለንም!!!ለዚህም የሰላም አባት የሆነው!ፈጣሪያችን ይረዳናል! ሀገራችንና ህዝባችንን ፈጣሪ ይባርክ! ማሳሰቢያ ከላይ በተገለጹት ሁለት መንገዶች ለሀገርና ለወገን የሚደረግ እርዳታ የአቅማችሁን በማድረግ ሰብአዊና ወገናዊ ሃላፊነታችሁን ለመወጣት የምትፈልጉ ሁሉ ለጉዳዩ የተዘጋጁትን የባንክ መረጃዎችን ከዚህ በታች ያስቀመጥንላችሁ መሆኑን በትህትና እንገልፃለን።

» Weiterlesen

ግድቡ የኔ ነው!

በመስፍን ጳውሎስ የህዳሴ ግድቡ ስራ መጠናቀቅ የአንድ ብሄር፣ሀይማኖት ወይም የፖለቲካ አመለካከት ያለው ህብረተሰብ ብቻ ፍላጎት ሳይሆን የሁሉም ኢትዮጵያውያን መሆኑ ግልጽ ነው።ከዚህ የግድብ ስራ ጋር የተያያዙ እንቅስቃሴዎች ላይ በሀገር ውስጥም ሆነ ከሀገር ውጭ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ተግባራዊ አስተዋጽኦ ለማድረግ ከፍተኛ ፍላጎት እንዳላቸው በያሉበት ከሚያደርጉት እንቅስቃሴዎች መገንዘብ ይቻላል።በዚሁ መሰረት በጀርመን አገር የህዳሴውን ግድብ ስራ ድጋፍ በሚመለከት የሚደረጉ እንቅስቃሴዎችን ማስተባበር የሚያስችል የተለያዩ ህብረተሰባችንን ከሚወክሉ ልዩ ልዩ ማህበራትና ታዋቂ ወገኖች የተካተቱበት ግብረሃይል ተቋቁሞ ስራ የጀመረ ሲሆን ግብረሃይሉ ከነደፋቸው ዘርፈ ብዙ የስራ ዕቅዶቹ አንዱ የህዳሴውን ግድብ አስመልክቶ በተለያዩ የታሪክ፣የጥናትና ሌሎች የስነፅሁፍ ውጤቶችን በመፅሔት መልክ በማሳተም ህብረተሰባችን ስለዓባይ ወንዝና ስለህዳሴ ግድብ ያለውን ግንዛቤ እንዲያሳድግና ከመፅሄቱም ሺያጭ የሚገኘውን ትርፍ ለህዳሴው ግድብ ስራ ማዋል እንዲያስችል ማድረግ በመሆኑ የተለያዩ በጀርመን የሚኖሩ ሀገር ወዳድ ወገኖችን በማስተባበር? * ግድቡ የኔ ነው * የሚል ርዕስ የተሰጠው መፅሔት ለህትመት እንዲበቃ ተደርጎ በየአካባቢው በሚገኙ የተለያዩ የኢትዮጵያውያን ማህበራት ተሰራጭቶ በመሸጥ ላይ ይገኛል።ስለዚህም ሀገሩን የሚወድ ዜጋ ሁሉ ትንሿን አስተዋፅኦ እንዲያደርግ አመቺ ሁኔታን የፈጠረ መሆኑን በመግለጽ የሙኒክና አካባቢው የኢትዮጵያውያን ኮሚዩኒቲ መጽሔቱን በደመቀ መርሀ ግብር አዘጋጅቶ ለማስተዋወቅና ለመሸጥ ዝግጅት እያደረገ መሆኑና እስከዚያው መጽሔቱን ለማከፋፈል ከወከላቸው የስራ አስኪያጅ ኮሚቴ አባላት መግዛት እንደሚቻል በማህበራዊ ሜዲያ ገልጿል።ስለዚህም ሀገር ወዳድ የሆንን ወገኖች ሁሉ ይህን „ግድቡ የኔ ነው“ የሚሰኝ መፅሐፀት ለራሳችንና ለሌሎች ወዳጆቻችን ገዝተን በስጦታነት በማበርከት አሻራችንን ለማሳረፍ እንድንችል ተጋብዘናልና ከግብዣው እንቋደስ። የኢትዮጵያ ህዝብ የህዳሴን ግድብ በመተባበርና በቁርጠኝነት ለፍፃሜ ያደርሳል!ፈጣሪ ኢትየጵያንና ህዝቧን ይባርክ! ከዚህ በታች *በዓባይ የኔ ነው* መጽሔት የቀረቡ አስተማሪና አስደማሚ ጽሁፎች መካከል ለናሙና ያህል በፎቶና በድምጽ አቅርበንላችኋል።

» Weiterlesen

የወንድማችን የአቶ ብሩክ ማሞ የመታሰቢያ ሃውልት ምርቃት

በሙኒክ ነዋሪ የነበረው ሀገር ወዳዱ ወንድማችን አቶ ብሩክ ማሞ ወደ ውድ ሀገሩ ወደ ኢትዮጵያ ሄዶ ባደረበት ድንገተኛ ህመም ከዚህ ዓለም መለየቱን አስመልክቶ ኮሚዩኒቲያችን አስተባባሪነት በኖቬምበር 14 ቀን 2020 እኤአ የፀሎትና የስንብት ስነስርዓት መደረጉ ይታወሳል ። በዚህ ስነስርዓት ላይ ከወዳጅ ጓደኞቹ ጥያቄ በመነሳት  ለወንድማችን የአቶ ብሩክ ማሞ የመታሰቢያ ሀውልት ማሰሪያ ይሆን ዘንድ በኮሚዩኒቲያችን በኩል የተሰበሰበውን (2000.00Euro) 100.000 (አንድ መቶ ሺህ ብር) ለቤተሰቦቹ አስተላልፈን አነሆ የሀውልቱ ስራ ተጠናቆ ቤተሰቦቹ በተገኙበት የተመረቀ መሆኑን የምናሳውቃችሁ ላሳያችሁት ወገናዊ ትብብር ከልብ በማመስገን  ነው። የወንድማችንን ነፍስ ይማር!  ለቤተሰቦቹና ለወዳጅ ዘመዶቹ መፅናናትን ይስጥልን!  በሙኒክ የኢትዮጵያውያን ኮሚዩኒቲ

» Weiterlesen

ከእኛ ወዲያ ለእኛ

በሙኒክ የኢትዮጵያውያን ኮሙዩኒቲ ማህበር በሰሜኑ የሀገራችን ክፍል በተከፈተው ህግን የማስከበር ዘመቻ ሳቢያ ጉዳት ለደረሰባቸው ነዋሪዎችና የመከላከያ ሰራዊት የማቴሪያልና የገንዘብ ድጋፍ የማድረጉ ስራ በሀገር ውስጥና ከሀገር ውጪ በሚኖሩ ሀገር ወዳድ ኢትዮጵያውያንና ትውልደ ኢትዮጵያውያን ከፍተኛ ርብርብ መደረጉንና እየተደረገ መሆኑን ይታወቃል ። በዚሁ መሰረት በሙኒክና አካባቢው የሚኖሩ ኢትዮጵያውያንና ትውልደ ኢትዮጵያውያን በሙኒክ የኢትዮጵያውያን ኮሙዩኒቲ „ከእኛ ወዲያ ለእኛ “ በሚል መርህ ባደረገላቸው የድጋፍ ጥሪ መሰረት 4000.00 € ይህም ወደ የኢትዮጵያ ብር ሲመነዘር በግምት ወደ 192,000 ሺህ የኢትዮጵያ ብር መሰብሰቡንና ይህም ገንዘብ ለዚሁ ጉዳይ በኢትዮጵያ ወደ ተከፈተው የባንክ ሂሳብ በቀጥታ ገቢ የተደረገ መሆኑን የኮሚዩኒቲው የስራ አስኪያጅ ኮሚቴ በኮሚዩኒቲው የማህበራዊ መገናኛ መድረክ ላይ የገንዘብ ድጋፍ ያደረጉትን ወገኖችን ስምና የክፍያ መጠን ከያዘ ዝርዝር መረጃ ጋር ግልጽነት በሚንጸባረቅበት መልኩ በማቅረብ አሳውቋል። ሀገራችን ኢትዮጵያን ከጥፋት ወገኖቻችን ከመከራ ይሰውርልን!ሀገራችን ኢትዮጵያ ታፍራና ተከብራ ለዘለዓለም ትኑር!

» Weiterlesen

ታሪክ ሰርቶ ማለፍ

በመስፍን ጳውሎስ  ውድ ኢትዮጵያውያንና ትውልደ ኢትዮጵያውያን የማክበር ሰላምታችንን እያቀረብን በምንኖርበት በጀርመን አገር በሙኒክ ከተማ ኗሪ የነበሩትና የሀገራችን የኢትዮጵያን ታሪክ ለኢትዮጵያውያንና ለሌሎች በአለም ዙሪያ ያሉ ሕዝቦች የማስተዋወቅ ስራ ለብዙ አመታት ሲሰሩ የነበሩት አቶ ግርማ ፍስሃ ዕድሜያቸው ደርሶ ጡረታ ሲወጡ ቀሪ ዘመናቸውን በሚወዷት ሀገራቸው እንዲሆን በመወሰን ከውድ ቤተሰቦቻቸውና ዘመዶቻቸው ጋር ሲኖሩ ቆይተው በህመም ምክንያት ከዚህ አለም በሞት እስከተለዩበት ድረስ ለሀገራቸው ባላቸው አቅምና ችሎታ የሚቻላቸውን ሁሉ ሲያደርጉ በመቆየታቸው ታሪክ ሲዘክራቸው ይኖራል ። አቶ ግርማ ፍስሐ ስላደረጉት የሀገርን ማስተዋወቅ ስራ በአንድ ወቅት ከታዋቂው የሸገር ሬዲዮ „ስንክሳር“ የሚሰኝ ዝግጅት ላይ „የሙኒኩ ተንቀሳቃሽ ቤተመዘክር“ በሚል ርዕስ የቀረበውን ዝግጅት ምናልባትም ከጥቂቶች በቀር  ብዙዎቻችን የማናውቀውን የወንድማችንን የአቶ ግርማ ፍስሀን ከፊል የህይወት ጉዞ፣ዝርዝር ሥራዎችና የሀገራችን ታሪክ እንድናውቅ ይረዳል ብለው ያመኑ ሀገር ወዳድ ወገኖች ከሰጡን አስተያየት በመነሳት እኛም በሀሳቡ ስላመንበት የወንድማችንን ህልፈት የ40ቀን መታሰቢያ በማድረግ በኮሚዩኒቲያችን ስም ልናካፍላችሁ ወደናልና ከዚህ ጽሁፍ በታች የተቀመጠውን የድምጽ ማጫወቻ  በመክፈት እንድትከታተሉት በማክበር ጋብዘናችኋል። በዚህ አጋጣሚም አቶ ግርማ ፍስሀን በጀርመን አገር በሙኒክ ከተማ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን እንደ ነዋሪ ብዙዎች እንደሚያውቋቸው ግልፅ ነው። ነገር ግን ይህን ያህል ጠለቅ ብሎ ያደረጉትን እንቅስቃሴና ጥረት  ለሀገራቸው ያበረከቱትን አስተዋፅኦ የሚያውቁ ምን ያህሉ ናቸው? በእውነትስ ብዙዎች „አብረን እንኖር ነበር እንጂ ለካ አናውቃቸውም ነበር! “ ሳያሰኛቸው ይቀራል? “ ብለን የአቶ ግርማ ፍስሀን ታሪክ መነሻ በማድረግ ሰፋ አድርግን አይተን የሚቀጥለውን ጥያቄ ለአንባቢያን እናቀርባለን በዓለም ዙሪያ በሚኖሩ የኢትዮጵያውያን ኮሙዩኒቲዎች መሀከል የሚገኙ እንደ አቶ ግርማ ፍስሃ ያሉ ብዙ ቁምነገርን የሰሩ ልምድና ዕውቀቱ ያላቸው ወገኖችን አብሮ ከመኖር በዘለቀ ምን ያህል ጠለቅ ብለን እናውቃቸዋለን? ማንም ሰው ቀኑ ሲደርስ ያልፋልና ከማለፋቸው በፊትስ ታሪካቸውን፣ያደረጉትን ጥረትና የሰሩትን ስራ፣የፈፀሙትን ገድል እንዲያካፍሉን ዕድሉን እያመቻቸንላቸውስ ነው? ስንቶችስ ብዙ ነገር ሰርተው ታሪካቸው ሳይታወቅ ትውልድ ሳይማርበት እንደ ዘበት አልፈዋል?  የሚለውን ጥያቄ ይህ ጽሁፍ ለሚያነቡ ሁሉ በማቅረብ ውድ ኢትዮጵያውያን በያሉበት በግልም ሆነ በተደራጀ መልክ ለጉዳዩ ትኩረት በመስጠት ሊወያዩበትና ሊንቀሳቀሱበት ይገባል እንላለን። በመጨረሻም ለጉዳዩ ትኩረት በመስጠት የአቶ የግርማ ፍስሃን የረጂም ዘመን ለሀገር የተደረገ ጥረት ወንድማችን በህይወት እያሉ ቃለመጠይቅ በማድረግ አቶ ግርማ ፍስሀ ከዚህ ዓለም በሞት ቢለዩም ታሪካቸው ለትውልድ ለማስተላለፍ ያስቻሉትን የሸገር ራዲዮ „ስንክሳር „ዝግጅት አዘጋጅ ጋዜጠኛ መኮንን ወ/አረጋይንና ባልደረባውን ወንጌላዊት ብርሃኑን እንደተቋምም የሸገር ሬዲዮ ጣቢያን በሙኒክ የኢትዮጵያውያን ኮሚዩኒቲ ስም ልናመሰግን እንወዳለን።የወንድማችንን ነፍስ ይማር!ለቤተሰቦቻቸው ፣ዘመድ ወዳጆቻቸው መፅናናትንና ጥንካሬን ይስጥልን!መልካም የማድመጥ ጊዜ እንመኛለን ።

» Weiterlesen

የአቶ ብሩክ ማሞ አጭር የሕይወት ታሪክ

2 Timothy 4:7-8 / 2ኛ ጢሞ 4 ፣ 7-8Ich habe den guten Kampf gekämpft, den Lauf vollendet, den Glauben bewahrt; hinfort liegt für mich die Krone der Gerechtigkeit bereit; መልካሙን ገድል ተጋድዬአለሁ፥ ሩጫውን ጨርሼአለሁ፥ ሃይማኖትን ጠብቄአለሁ፤ ወደ ፊት የጽድቅ አክሊል ተዘጋጅቶልኛል፥ I have fought the good fight, I have finished the race, I have kept the faith. Henceforth there is laid up for me the crown of righteousness, which the Lord, the righteous judge, will award to me on that day በወ/ሮ እናኑ ጌታሁን የቀረበ ወንድማችን አቶ ብሩክ ማሞ ወይም በክርስትና ስሙ ተክለ አረጋዊ ሰኔ 6 ቀን 1955 ዓ.ም በአዲስ አበባ ከተማ ተወለደ። በአዲስ አበባ ቢወለድም የወጣትነት እድሜዉንና ትምህርቱን የተከታትለው በቀደሞ ስሙ በጅባትና ሜጫ አውራጃ በአምቦ ክተማ ነዉ። እንደማንኛውም ህጻን በዚያን ዘመን በቄስ ት/ቤ ፊደል ቆጥሮ የአንደኛ ደረጃ ትምህርቱን በአምቦ ት/ቤት በጥሩ ሁኔታ ስላጠናቀቀ፣ የ2ተኛ ደረጃ ትምህርቱን በአዲሰ አበባ ጄኔራል ዊንጌት አዳሪ ት/ቤት ለመማር እድል አገኝቶ ለ4 ዓመታት ትምህርቱን ተከታትሏል። በጥሩ ውጤትም አጠናቋል።  

» Weiterlesen

ከሰው ማሣ አትጨድ!

ተዋናይ ፣ አዘጋጅ ፣ ገጣሚ እና አርቲስት ፣ የጣይቱ የባህል ማዕከል በዋሺንግተን ዲሲ መስራች አለም ፀሃይ ወዳጆ ከሰው ማሣ አትጨድ! ከሰው ማሳ አትጨድ …የንጥቂያ ከፍታ መሬት ታውላለች፤እያንዳንዷ ውጤት …እያንዳንዷ ፍሬ ዋጋ አስከፍላለች፡ጥረህ ግረህ ብላ …እንደ መፅሐፉ ቃል፡ዛሬም ባይሆን ነገ የሰው ወዙ ያንቃል፤አፈሩን ጎልጉሎ … ቆፍሮ አረስርሶ፡ዘርቶ ተንከባክቦ ….ከእንቅልፉ ቀንሶ፤ለዝናብ አንጋጦ ….ፀሐይን ተማልዶ፡መዳፉን አሻክሮ …ልምዱን አዋሕዶ፤በውኑም በእንቅልፉም ፡ሲያስብ ከርሞበታል፡ፍሬው እስኪያፈራ ፡ ሥቃይ ቆጥሮበታል፤ከሰው ማሳ አትጨድ ! …በጨለማ ተገን ፤ እንዳይቀጨው አውሬ፡እንዳያዳባየው ፡ ረግጦ ተራምዶበትግድ አይሰጠው ጥሬ …አጥሮ ጠብቆት ነው ውጤት ሆኖ አብቦ ይህ ያየኸው ዛሬ፤እያንዳንዷ ውጤት …እያንዳንዷ ፍሬ ዋጋ አስከፍላለች፡ከሰው ማሳ አትጨድ …የንጥቂያ ከፍታ መሬት ታውላለች፤ጥረህ ግረህ ብላ …እንደ መፅሃፉ ቃል፡ዛሬም ባይሆን ነገ …. የሰው ወዙ ያንቃል፤በግንባር ፡ በላብህ በጉልበትህ ጥረት ፡በራስህ ተመንደግ በድካምህ ውጤትከሰው ማሣ አትጨድ…ዝም ብሎ አላፈራም እንዲያው እንደዘበት … ዘለህ አትፈሰው…ንቀህ ወይ ዘንግተህ የደከመበትን የፈጠረውን … ሰው ፤በየቱም ሙያ መስክ …በምንም ሥራ ላይደክመህ መመንደግ ነው … ከልብ የሚያረካው .. ስትውል ከበላይጤና ተገብሮ ተስፋ ተሰንቆ ፡በቁር በሐሩሩ …. ተጥሎ ተወድቆ፤የጋሬጣ ፍቀት … ያደማ እሾህ ታልፎ ፡የለማ ፍሬ ነው …ከዕድሜ ላይ ተቀርፎ ፤ከሰው ማሣ አትጨድ !

» Weiterlesen

ለውድ የኢትዮጵያውያን ኮሚዩኒቲ በሙኒክ አባላት በሙሉ !

በቅድሚያ አክብሮታዊ ስላምታችንን እናቀርባለን! ኮሚዩኒቲያችንን ለማጠናከር በሚደረገዉ እንቅስቃሴ ውስጥ ማኀበሩ የራሱ ድህረ ገጽ (Website) እንዲኖረው ታስቦ ሶሰት አባላት ያሉበት አንድ ኮሚቴ ከኮሚዩኒቲው የሥራ አስኪያጅ ኮሚቴ በተሰጠው ኃላፊነት መሰረት ዕቅዱን ተግባራዊ ለማድረግ በትጋት በመንቀሳቅሰ ላይ ይገኛል። ይህ አንቅስቃሴም ውጤታማ ሆኖ እነሆ ኮሚዩኒቲያችን የራሱ የሆነ ድህረ ገፅ (Website) መክፈቱን የምናበስራችሁ በታላቅ ደስታ ነው!  ወደዚህ ውጤት ልንደርስ የቻልነው ከኢትዮ ሚዪኒክ ( http://www.ethiomunchen.de ) ድህረ ገጽ አዘጋጅ በተደረገልን ትብብር በመሆኑ የኮሚኒቲያችን አባልና የኢትዮሙኒክ ድህረ ገጽ ባለቤትን አቶ ወርቅነህ ክፍሌን ላደረጉልንና ወደፊትም ለሚያደርጉት እገዛና ተሳትፎ ይህን የሥራ ኃላፊነት ተቀብሎ በሚንቀሳቀሰው ኮሚቴና በእናንተ በኮሚዩኒቲው አባላት ስም ከፍ ያለ ምስጋና እናቀርባለን። በድህረ ገፁ ላይ ምን ተግባራዊ ሆኗል?   ምንስ ሊስተናገድ ይችላል?  የማሀበሩ ታሪክ፣ መረጃዎችና የተቀነባበሩ ዝግጅቶች ይሰነዱበታል፣ ይዘገቡበታል። የአባልነት ክፍያና ሌሎች ክፍያዎችን ለማድረግ የኮሚዩኒቲው የባንክ አካውንት በቀላሉ ይገኛል። አባል መሆን የሚፈልጉ በሙኒክ ከተማ ነዋሪ የሆኑ ኢትዮጵያውያንና ትውልደ ኢትዮጵያውያን የተዘጋጀውን የአባልነት ቅጽ ኦንላይን (online) በመሙላት ከአመራር አካሉ ጋር በቀላሉ ግንኙነት ለመጀመር ይችላሉ። አባላትና ቤተሰቦቻቸው ስለሀገራችን ስለኢትዮጵያ ታሪካዊና ወቅታዊ ሁኔታዎች እንዲሁም ሌሎች የተለያዩ ጠቃሚ መረጃዎችን በማግኘት እንዲያነቡ፣ እንዲጽፉና መሰል ተሳትፎ እንዲያደርጉ የማስቻል እቅድ ይዞ በመነሳት ተግባራዊ ተደርጓል! ኮሚዩኒቲያችንን ከመሰል ማኀበራትም ሆነ ከሌላው ዓለም ጋር ለማገናኘት ድልድይ ይሆናል። በመሰረቱ ይህ ድህረ ገፅ ሊያድግና ተጠናክሮ ሊቀጥል የሚችለው በተወስኑ ሰዎች ጥረት ብቻ ሳይሆን በዋናነት በአባላቱ ተሳትፎ ነውና ተሳትፏችሁን እንድታጎለብቱ እየጋበዝን ከዚህ በታች የተቀመጠውን ሊንክ በመጠቀም ድህረ ገፁን (Website) መጎብኘትና የተለያዩ ሕብረተሰባችንን ሊያስተምሩ፣ ሊያነቁና ሊያዝናኑ የሚችሉ ሰነጽሁፍ፣ ግጥምና ምስሎች፣ ተንቀሳቃሽ ምስሎች፣ የመሳስሉትን ከዚህ በታች ከድህረ ገጹ ጋር በተቀመጠው የኢሜል አደራሻ በመላክ መሳተፍ የምትችሉ መሆኑን በአክብሮት እንገልፃለን።  ኢትዮጵያንና ህዝቦቿን ፈጣሪ ይባርክ! እናመሰግናለን ድህረ ገፃችን: http://ethiomunichcommunity.de/            E-Mail:       info@ethiomunichcommunity.de ማሳሰቢያ ማሳሰቢያበዚህ ድህረ ገፅ (Website) ላይ የሚወጣ ማናቸውም አስተያየት፣ ጽሁፍ፣ ግጥምና ምስል የማንኛውንም የህብረተስብ ክፍልም ሆነ ግለሰብ ስብዓዊ ክብርና መብት የሚጠብቅ፣ እኩልነትን የሚቀበል በጋራ መንፈስ ላይ ተመርኩዞ የሃገርን አንድነትና ሉአላዊነት የሚድግፍ ሃሳብ ብቻ መሆን እንዳለበት ከወዲሁ ግልጽ ማድረግ እንወዳለን።

» Weiterlesen
1 2